የትምህርት ሚኒስቴር በዚህ ዓመት 200 ት/ቤቶች በአማራ እና አፋር ክልሎች እንደሚገነቡ አስታወቀ።
የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የኮሚዩኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ አመለ ወርቅ ህዝቅኤል በት/ቤት ግንባታዎቹ መንግስታዊ ያልሆኑ የረድኤት ተቋማት እያገዙ መሆናቸውን ተናግረዋል። ሊገነቡ ከታቀዱት ት/ቤቶች የአምስቱ ግንባታ ተጀመሯልም ተብሏል።
ህብረተሰቡ በ9222 ለትምህርት ተቋማቱ ግንባታ ተስትፎ እንዲያደርግም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጠይቋል።
የኢትዮጵያ አርኪቴክቶች ማህበርም ሊገነቡ የታሰቡትን ት/ቤቶች ዲዛይን አጠናቆ ማስረከቡ ተገልጿል።
በአማራ፣ አፋር፣ ኦሮሚያ እና ቤኒሻንጉል በሺዎች የሚቆጠሩ ት/ቤቶች በጦርነት መውደማቸው ይታወሳል።
በብሩክ ያሬድ
2022-11-04
