ለሳምንታት ተቋርጦ የቆየው በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይ የሚገኙ ዜጎችን የመመለስ ሥራ ኅዳር 12 እንደሚጀመር ብሄራዊ አስመላሽ ኮሚቴው አስታወቀ።
የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር እንዳስታወቀው ተመላሾች የሚያርፉባቸው መጠለያዎች ብሄራዊ ኮሚቴው አዘጋጅቷል ።
ብሄራዊ ኮሚቴው ከአሁን ቀደም ባስተባበራቸው የአውሮፕላን በረራዎች 71 ሺህ 697 ፍልሰተኞች ወደ አገራቸው የመለሰ ሲሆን፣ በቀጣዩ ዙር ለመመለስ የታቀደው የመጨረሻዎቹን 30 ሺህ 303 ፍልሰተኞች ነው።
በብሩክ ያሬድ
2022-11-09
