ሀገሬ ቲቪ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ 25 ቢሊዮን ዶላር የማግኘት ዕቅድ መያዙ ተገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኢትዮጵያ አቆጣጠር 2027 25 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ለማግኘት አቅዶ እየሰራ መሆኑን ገለጸ ።

ለዚህም የበረራ መዳረሻውንና የአውሮፕላን ቁጥሩን በእጥፍ ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ተናግረዋል።

65 ሚሊዮን ተሳፋሪዎችን እና 3 ሚሊዮን ቶን ጭነት የማጓጓዝ አቅም እንዲኖረው እንቅስቃሴ መጀመሩም ተገልጿል ።

ይሄንን ዕቅዱን ለማሳካት አውሮፕላኖቹን ወደ 271 ለማሳደግ እየሰራ ስለመሆኑም ዋና ስራ አስፈጻሚው ተናግረዋል።

በአብርሃም በለጠ
2022-11-24