
ሾልኮ በወጣ አንድ ሪፖርት ራማፎዛ ስልጣናቸውን ያለ አግባባ መጠቀማቸውን እንዲሁም የጸረ ሙስና ህጉን መጣሳቸውን ያመልካታል ተብሏል።
ፕሬዝዳንቱ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2020 በግል የእርሻ መሬታቸው የተደበቀ ሕገ ወጥ 4 ሚሊዮን ዶላር እንደተገኘ ተሰምቷል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ በቁጥጥር ለዋሉ ግለሰቦች ጉቦ በመስጠት ጉዳዩን በዝምታ እንዲታለፍ ጥረት አድርገዋል በሚል ነው የተጠረጠሩት ።
ፕሬዝዳንቱ በበኩላቸው ይህን ድርጊት አልፈጸምኩም ብለዋል ። በጉዳዩ ላይ የሃገሪቱ ፓርላማ በሚቀጥለው ሳምንት ጉዳዩን መርምሮ ራማፎሳ ላይ ክስ የመመሰረቱ ሂደት ይጀመር ወይም አይጀመር የሚለውን ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ቢቢሲ አስነብቧል።
በወንድምአገኝ አበበ
2022-12-01