ሀገሬ ቲቪ

ዲሞክራቶች በሴኔት ያለቸውን የበላይነት አረጋገጡ

በጆርጂያ ሲወዳደሩ የነበረሩት ራፋኤል ዎርኖክ አሸናፊ መሆናቸውን ተከትሎ ዲሞክራቶችን በሴኔት አብላጫውን መቀመጫ ያዙ ።

ዎርኖክ ከሪፕብሊካኑ ተወካይ ኸርሸል ዎልከር የገጠማቸውን ከባድ ፉክክር በበላይነት ማሸነፉቸውን ተከትሎ ዲሞክራቶች በአሜሪካ ምክር ቤት ያላቸውን የመቀመጫ ቁጥር ከፍ አድርገዋል።

በዚህም ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ፓርቲያቸው በላይኛው ምክር ቤት 51 ለ 49 በሆነ ውጤት እየመራ ይገኛልል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል።

በባለፈው ወር በአሜሪካን በታችኛው ምክር ቤት ጥቂት ወንበሮችን ብቻ በመያዛቸው ዲሞክራቶች ዝቅተኛ ግምት ተሰጥቷቸው እንደነበር ይታወሳል።

በዮሴፍ ከበደ
2022-12-07