
የተባበሩት መንግስታት ድርጀት እና የአረብ ሊግ ሃገራት ባደረጉት ስብሰባ በሱማሊያ እየቀጠለ የሚገኘው ድርቅ አደገኛ ደረጃ ሊደርስ ይችላል ሲል አስጠንቅቀዋል ።
ሱማሊያ በተደጋጋሚ ጊዜ እየገጠማት የሚገኘው የዝናብ እጥረት በሃገሪቱ ለተከስተው ደርቅ ምክንያት ሆኗል ተበሏል ።
በሱማሊያ ከአጠቃላይ 15 ሚልዮን ህዝብ ግማሽ ያህሉ በድርቅ ሳቢያ በምግብ እጥረት ውስጥ እንደሚገኝ ተጠቅሷል ።
1.3 ሚሊየን የሚደርሱ ዜጎች ደግሞ ከመኖሪያቸው ተፈናቅለዋል ። በቀጣዩ አመት መጨረሻም 6.7 ሚሊዮን ሕዝብ ከፍተኛ የምግብ እጥረት ሊገጥማቸው ይችላል ሲሉ ተመድ እና የአረብ ሊግ ሃገራት ሰጋታቸውን ገልጸዋል።
በወንድምአገኝ አበበ
2022-12-08