የቻይና መንግስት የኢትዮጵያ ምርቶች ከቀረጥ ነጻ እንዲገቡ ፈቀደ። ንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር እንዳስታወቀው ቻይና ለ1 ሺህ 644 የሀገራችን ምርቶች ከቀረጥ እና ኮታ ነጻ እንዲገቡ ፈቅዳለች።
ከቻይና የተሰጠው የገበያ ዕድሉ ኢትዮጵያ ላይ የሚጥለው ምንም ዓይነት ግዴታ እንደማይኖርም ተጠቁሟል።
የኮታ እና ቀረጥ ነጻ ፍቃድ የተሰጣቸው 1 ሺህ 644 ምርቶች ወደቻይና ከሚነገድባቸው 6 ሺህ 422 ምርቶች መካከል ነው።
በአብርሃም በለጠ
2022-12-12
