በሰሜኑ የኢትዮጵያ ጦርነት ጉዳት የደረሰባቸውን የጤና ተቋማት በምዕራፍ ለመጠገን አቅድ መያዙን የጤና ሚኒስቴር አሳወቀ፡፡
ተቋሙ የወባ ወረርሺኝ በ 11 ክልሎች መከሰቱንም ባቀረበው የሰድስት ወራት አፈጻጸም ግምገማ ላይ ገልጿል ።
የጤና ሚንስቴር ለጤና፣ ማህበራዊ ልማት ፣ባህል እና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሰድስት ወራት አፈጻጸም ሪፖርትን ዛሬ አቅርቧል ። ቋሚ ኮሚቴው የቀረበውን ሪፖርትም አድምጧል ።
ኮሚቴው ባደርገው የመሰክ ምልከታ በሰሜኑ ጦርነት ጉዳት የደረሰባቸው የጤና ተቋማትን ተመለክቷል ። ኮሚቴው በጦርነቱ ጉዳት የደርሰባቸውን የጤና ተቋማትን ለመገንባት የጤና ሚንስቴርን ዝግጁነት ጠይቋል።
የጤና ሚንስትሯ በበኩሏ የወደሙ የጤና ተቋማትን መልሶ ስራ ለማስጀመር እየተደረጉ ያሉ ተግባራት ላይ ገለጻ አድርገዋል ።
በተያዘው አመት በወረርሺኝ መልክ ከተከስቱ በሽታዎች መሃከል የ ወባ በሽታ አንዱ ነበር ። ሚንስቴሩ በሪፖርቱ የወባ ወረርሺኝ ከ ቤኒሻንጉል ክልል ወጪ በሁሉም የሃገሪቱ ክልሎች መከሰቱ ተገልጻል ።
ቋሚ ኮሚቴም በዚህን መጠን የተከሰተውን የወባ ወረርሺኝ ለመከላከል ስለተወሰወሰደው እርምጃ ጥያቄ አንስቷል ። የጤና ሚንስቲሯ በተነሳው ጥያቄ ላይም ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል።
ቋሚ ኮሚቴው ተቋሙ ባቀረበው ሪፖርት ጥሩ ጎኖች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ እና ክፍተት የታየባቸው ስራዎች በቀጣይ በትኩረት እንዲሰሩ አጸኖት ሰጥቷል ።
በወንድምአገኝ አበበ
2023-02-01
