ሀገሬ ቲቪ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሕወሃትን ከሽብርተኝነት ስያሜ አንስቷል

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሕወሃትን ከሽብርተኝነት ስያሜ አንስቷል፡፡

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባደረገው 1ኛ ልዩ ስብሳባው ሕወሃትን ከሽብርተኝነት ስያሜ ለማንሳት የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ የውሳኔ ቁጥር 12/2015 በ61 ተቃውሞ በ5 ድምፅ ታቅቦ በአብላጫ ድምፅ አፅድቋል፡፡

በሕወሃትና በፌደራል መንግሥቱ በኘሪቶሪያ የተደረገውን ሥምምነት ለማፅናት ሕውሃትን ከሽብርተኝነት ስያሜ ማንሳት አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑን የውሳኔ ሃሳብ በቀረበበት ወቅት ተነስቷል፡፡


2023-03-22