ሀገሬ ቲቪ

መንግሥት የግብርናውን ዘርፍ መረጃዎች በማዘመን ሁሉም አርሶአደር እኩል መረጃ እንዲኖረው ለማድረግ ብሄራዊ ዲጅታል የግብርና ኤክስቴንሽን እና ምክር አገልግሎት ፍኖተ-ካርታ አዘጋጅቷል።

መንግሥት የግብርናውን ዘርፍ መረጃዎች በማዘመን ሁሉም አርሶአደር እኩል መረጃ እንዲኖረው ለማድረግ ብሄራዊ ዲጅታል የግብርና ኤክስቴንሽን እና ምክር አገልግሎት ፍኖተ-ካርታ አዘጋጅቷል።

የብሄራዊ ዲጅታል የግብርና ኤክስቴንሽን እና ምክር አገልግሎት ፍኖተ-ካርታ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ይፋ የተደረገ ሲሆን መድረኩ የተዘጋጀው ግብርና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት በመቀናጀት ነው፡፡

በግብርና ሚኒስቴር የእርሻና ሆርቲካልቸር ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር መለሰ መኮንን መንግሥት ስለግብርና መረጃዎችን ዲጂታይዝድ በማድረግ ሁሉም አርሶአደር እኩል መረጃ እንዲኖረው በማድረግ የግብርናውን ዘርፍ እያዘመነው ይገኛል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ጀነራል ዳይሬክተር ዶ/ር ማንደፍሮ ንጉሴ የብሄራዊ ዲጅታል የግብርና ኤክስቴንሽን እና ምክር አገልግሎት ፍኖተ-ካርታ አላማው የአርሶ አደሩን ምርታማነት መጨመር፣ ሴት እና ወጣት አርሶ አደሮችን ማብቃት እንዲሁም ምግብና ስርዓተ- ምግብን ማሻሻል እንደሆነም አብራርተዋል፡፡

በብሩክታዊት አስራት
2023-03-27