ከሰኔ 1 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በመላ ኢትዮጵያ የዲጂታል የነዳጅ ግብይት እንደሚጀመር ተጠቆመ፡፡
ዛሬ በመዲናዋ ለሙከራ የተጀመረው የዲጂታል ግብይት በሁሉም ተሽከርካሪዎች እና በሁሉም ማደያዎች ተግባራዊ እንደሚሆን የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር (ዶ/ር) አለሙ ስሜ ተናግረዋል።
ግብይቱ በዲጂታል መንገድ መከናወኑ ምርት እንዳይባክን እና የተሳለጠ ግብይት እንዲኖር እንደሚያደርግ ተጠቁሟል።
በቅርቡም የትራንስፖርት ትኬት በዲጂታል እንደሚጀመር ተነግሯል፡፡
በብሩክታዊት አስራት
2023-03-31
