የቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝደንት ጫላ ዋታ (ዶ/ር) በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለዋል፡፡
ጫላ ዋታ (ዶ/ር) በተደረገባቸው ምርመራ ከ23 ሚሊየን ብር በላይ ከዩኒቨርሲቲው አካውንት ወደ ድርጅታቸው ያለ አግባብ ገቢ ያደረጉ የተገለፀ ሲሆን፤ 195 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ያለ አግባብ ግዥ እንዲፈፀም ማድረጋቸው ተረጋግጧል ተብሏል።
በተጨማሪም በ116 ሚሊዮን ብር በግል ተቋራጭ ሥም 14 ተሸከርካሪዎችና ማሽነሪዎች እንዲፈፀም ማድረጋቸው ተጠቁሟል፡፡
በዩኒቨርስቲው ገንዘብ የተገዙ ተሸከርካሪዎችና ማሽነሪዎች ባለቤትነታቸው በግል ድርጅት ሆኖ መገኘቱም ተመላክቷል፡፡
አባሉ የመንግሥት ግዥ ሕግ ከሚፈቅደው ሕግ ውጪ፣ በግላቸው ለመሰረቱት ቢ ኤች ዩ ኮንሰልታንስ የተባለ የንግድ ድርጅት በግንባታ አማካሪነት በመቅጠር በቀጥታ ግዥ በመፈፀም በመንግሥት ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል ተብሏል፡፡
በዚህም ምክንያት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 13ኛ መደበኛ ጉባኤ፤ ያለ መከሰስ መብታቸውን ያነሳባቸው ጫላ ዋታ (ዶ/ር) በፖሊስ ቁጥጥር ሥር መዋላቸው ታውቋል፡፡
በአብርሃም በለጠ
2023-04-04
