አሜሪካ የጦር መርከቦቿን በታይዋን የባህር ወሽመጥ ማስጠጋቷ ተገለፀ፡፡
አሜሪካ የቻይናን ወታደራዊ ልምምድ ተከትሎ በታይዋን የባህር ወሽመጥ በኩል የባህር ኃይሏን ማሰማራቷ ተነግሯል።
በርኬ-ክላስ የሚመራ አንቲ ሚሳዬል የጫኑ 7 የጦር መርከቦቿን ማስጠጋቷ ነው የተነገረው።
ቻይናም የአሜሪካንን የጦር መርከብ በባህር ወሽመጦቹ በኩል ሲያልፉ አስተውያለሁ ብላለች፡፡
የቻይና መከላከያ ቃል አቀባይ ኮሌኔል ሺ ዩ በባህር ወሽመጡ አካባቢ ያሉ የቻይና ወታደሮች ሁሌም በተጠንቀቅ ላይ መሆናቸውን አሳውቀዋል።
ወታደሮቹ ለሀገራቸው ሉዓላዊነት እና ደህንነት እንዲሁም የህዝባቸውን ሰላም ለማስጠበቅ እንደሚታገሉ ተናግረዋል ሲል የዘገብው አልጀዚራ ነው።
በማህሌት አማረ
2023-04-17
