ሀገሬ ቲቪ

በቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን መከስከስ ሕይወታቸው ያለፉ ሰዎች ቤተሰቦች አውሮፕላኑ መሬት ላይ ከመከስከሱ አስቀድሞ ተጓዦቹ ለደረሰባቸው ሕመም እና ሰቀቀን ካሳ ሊጠይቁ ይችላሉ ተባለ።

በቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን መከስከስ ሕይወታቸው ያለፉ ሰዎች ቤተሰቦች አውሮፕላኑ መሬት ላይ ከመከስከሱ አስቀድሞ ተጓዦቹ ለደረሰባቸው ሕመም እና ሰቀቀን ካሳ ሊጠይቁ ይችላሉ ተባለ።
Br> ይህንን ያሉት በአሜሪካ ኤሊኖይስ ዳኛ የሆኑት ጆርጅ አሎንሶ ናቸው።
Br> ከአራት ዓመታት በፊት የተከሰከሰው እና የኢትዮጵያ ንብረት የነብረው አውሮፕላኑ የ157 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ የአውሮፕላን አምራቹ ቦይንግ ተጓዦች ላይ የደረሰውን ህመም እና ሰቀቀን ከግምት ውስጥ አላስገባም ነበር ተብሏል።
Br> ዳኛው አውሮፕላኑ ላይ በተፈጠረው አደጋ በጉዳት እና ሰቀቀን ተጓዦች ለመሞታቸው አንዱ ምክንያት ሊሆን ይችላል ብለዋል።
Br>

በአብርሃም በለጠ
2023-05-31