ሀገሬ ቲቪ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በፈረንጆቹ 2035 የአውሮፕላኖቹን ብዛት 271 ለማድረስ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በፈረንጆቹ 2035 የአውሮፕላኖቹን ብዛት 271 ለማድረስ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ፡፡

አሁን ላይ ወደ 140 በሚጠጉ አውሮፕላኖች እየተሰራ መሆኑን ተነግሯል፡፡

ከሰኔ 5 ቀን ጀምሮ አየር መንገዱ ከሚያዛቸው 29 አውሮፕላኖች ማለትም 17 የ737 ማክስ፣ አምስት 777ኤፍ ኤስ፣ አንድ 787-9 እና ሥድስት ኤርባስ ኤ350-1000 አውሮፕላኖች ይገኙበታል ተብሏል፡፡

በአፍሪካ 63 ዓለም አቀፍ መዳረሻዎች ያሉት አየር መንገዱ፥ በአሁኑ ወቅት ያለውን 20 አውሮፕላን ማረፊያዎች ወደ 27 እንደሚያሳድግም ነው የተጠቆመው፡፡

በብሩክታዊት አስራት
2023-06-09