ዛሬ በመላው ኢትዮጵያ 500 ሚሊየን ችግኝ የመትከል መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው።
በዚህ መርሃ-ግብር ሚንስትሮችና የክልል ፕሬዝደንቶች ሂደቱን በበላይነት በማስተባበር ላይ ናቸው፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለዚሁ ስራ ሲባል ዛሬ ከንጋቱ 11:00 ጀምሮ የአንበሳ አውቶብስ እስከ ምሽት ነፃ ትራንስፖርት እንዲሰጥ አድርጓል።
መርሃ ግብሩ በመንግስት የመገናኛ ብዙሃን ሰፊ ሽፋን ተሰጥቶታል።
በማህሌት አማረ
2023-07-17
