ሀገሬ ቲቪ

ወደ ውጭ ገበያ ከተላከ ቡና 1 ነጥብ 3 ቢሊየን ዶላር ገቢ ተገኘ፡፡

ወደ ውጭ ገበያ ከተላከ ቡና 1 ነጥብ 3 ቢሊየን ዶላር ገቢ ተገኘ፡፡

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ240 ሺህ 369 ቶን በላይ ቡና ወደ ውጪ ገበያ ተልኮ ከ1 ነጥብ 3 ቢሊየን በላይ የአሜሪካ ዶላር ገቢ መገኘቱን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል፡፡

በበጀት ዓመቱ ከ360 ሺህ ቶን በላይ ቡና ወደ ውጭ በመላክ 1 ነጥብ 8 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ እንደነበር ባለስልጣኑ ገልጿል፡፡

ገቢው ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር ቅናሽ ማሳየቱ ተነግሯል፡፡

በብሩክታዊት አስራት
2023-07-19