ሀገሬ ቲቪ

የ2016 በጀት ዓመት በጀመረ 12 ቀናት ውስጥ በሀገር አቀፍ ደረጃ 52 ሺህ 129 አገልግሎቶች በኦንላይን መሰጠታቸውን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የ2016 በጀት ዓመት በጀመረ 12 ቀናት ውስጥ በሀገር አቀፍ ደረጃ 52 ሺህ 129 አገልግሎቶች በኦንላይን መሰጠታቸውን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ይህ አገልግሎት የተሰጠው በ2016 በጀት ዓመት ከሐምሌ 1 ጀምሮ ባለፉት 12 ቀናት ብቻ መሆኑም ተመላክቷል፡፡

ሚኒስቴሩ በ2015 በጀት ዓመት 1 ሚሊዮን 496 ሺህ የንግድ ምዝገባና ፍቃድ አገልግሎቶች መሰጠታቸውን ተናግሯል፡፡

በ2016 በጀት ዓመት በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የኦንላይን አገልግሎቶችን ወደ 90 ከመቶ ለማሳደግ እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡

በብሩክታዊት አሥራት
2023-07-21