የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት የንግዱን ማህበረሰብ የሚያስፈራሩ ግለሰቦች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳሰበ።
አንዳንድ ግለሰቦች ወንጀሎቹን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚጠበቅባቸውን የዜግነት ኃላፊነት ከመወጣት ይልቅ፤ ሀሰተኛ የማደናገሪያ ና ማስፈራሪያ ስልቶችን በመጠቀም የንግዱን ማህበረሰብ በማሸበር ጥቅም የማጋበስ ዝንባሌ እንደሚታይ አገልግሎቱ ጠቁሟል፡፡
ስለሆነም የንግዱን ማህበረሰብ በማስፈራራት በወንጀል ድርጊት ለመጠቀም የሚሞክሩ ግለሰቦችን ከተመለከቱ ለፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት በስልክ ቁጥር 011-812-8261 በመጠቆም የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርቧል።
በዚህ የወንጀል ድርጊት ያለ አግባብ ለመጠቀም በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኙ አንዳንድ ግለሰቦችም ከወንጀል ድርጊታቸው እንዲታቀቡ አሳስቧል።
በሙሉጌታ በላይ
2023-07-25
