ሀገሬ ቲቪ

የኢትዮጵያ የክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ በ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት ከ271 ሚሊዮን ብር በላይ አትርፌያለሁ አለ።

የኢትዮጵያ የክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ በ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት ከ271 ሚሊዮን ብር በላይ አትርፌያለሁ አለ።

ይህ ገቢው ከባለፈዉ ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር 27 ነጥብ 8 በመቶ ብልጫ እንዳለው አስታውቋል።

የኢንተርፕራይዙ የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያዉ ስድስት ወራት የትርፍ አፈፃፀም ከዕቅዱ ጋር ሲነጻጸርም 111 በመቶ ድርሻ እንዳለው ነው የገለጸው።

በብሩክታዊት አሥራት
2024-02-02