
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አገልግሎቱ መስተካከሉን ገለፀ።
በባንኩ መረጃ ማስተላለፊያ የፋይበር ኦፕቲክስ ገመድ ላይ ተፈጥሮ የነበረው ችግር በመስተካከሉ በቅርንጫፎች፣ በኢንተርኔት ባንኪንግ፣ በሞባይል ባንኪንግ፣ እንዲሁም በሲቢኢ ብር ላይ ተቋርጦ የነበረው አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ የጀመረ መሆኑንም ባንኩ ገልጿል።
ተፈጥሮ ለነበረው የአገልግሎት መስተጓጎልም ይቅርታ ጠይቋል።
በብሩክታዊት አሥራት
2024-02-20