ሀገሬ ቲቪ

ከ8 ሺ በላይ የብልጽግና ፓርቲ አባላት ላይ እርምጃ ተወሰደ

ባለፉት ስድስት ወራት ከ8 ሺ በላይ የብልጽግና ፓርቲ አባላት ላይ እርምጃ መወሰዱን ጠቅላይ ሚንስቴር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ተናገሩ።

ጠቅላይ ሚንስቴሩ ይህ የተናገሩት ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ውይይት ባደርጉበት ወቅት ነበር።

ፓርቲው ከ8 ሺ በላይ የሚሆኑ አባላቱ ላይ የእስር፣ የመባረር እና ከደረጃ ማውረድ ውሳኔ ማሳለፉን ተናግረዋል።

ከፓርቲው አባልነት የተነሱ ግለሰቦች ተገቢ ባልሆነ፣ እንቅስቃሴ ውስጥ የተሳተፉ እንደሚገኙ ገልጸዋል።

በወንድማገኝ አበበ
2024-04-03