የዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት አይኦኤም በጦርነት ከምትታመሰው የመን በእስር ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እየመለሰ መሆኑ ተስምቷል።
በያዝነው በፈረንጆቹ ወር በመጀመሪያዎቹ ሶስት በረራዎች ከ600 በላይ ኢትዮጵያውያን ከየመን ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውም ተጠቁሟል።
አይኦኤም በሚቀጥሉት ሳምንታት ከየመን ወደ ኢትዮጵያ ተጨማሪ በረራዎች እንደሚደረጉ ጠቅሶ መመለስ የሚፈልጉትን ሁሉንም ኢትዮጵያውያንን ለመድረስ ግን ድጋፍ ያስፈልገኛል ብሏል።
በሚቀጥሉት ወራትም ተጨማሪ 75,000 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች አሁን ባለው ኦፕሬሽን ይመለሳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በመቅደስ እንዳለ
2022-05-25
