ሀገሬ ቲቪ

የተሰረቀችው ሞተር መጨረሻ

እስቲ ዛሬ ከጥያቄ እንጀምር፤ አንድ የሚጠቀሙበት ንብረት ቢጠፋዎት ምን ያደርጋሉ?

ያው እንደ ሁሉም ሰው ይመለከታቸዋል ለሚሏቸው የፀጥታ አካላት የጠፍቶብኛል ይፈለግልኝ ማመልከቻ ማስገባት እና መጨረሻውን አብሮ መጠበቅ ሊሆን ይችላል መልሶት። እንዲሁም ከወዳጅ ዘመዶ ጋር ይገኝነታል ያሉትን ቦታ ሁሉ ማካለል፤ ከዛም ሻገር ሲል ወሮታ ከፋይ ነኝ ንብረቴን አፋልጉኝ ሲሉ በመገናኛ ብዙኃን ሳይቀር መለፈፍ።

ይህንን ሁሉ አድርገው የተሰረቀቦትን ንብረት በፍፁም በማይጠብቁት ቦታ ላይ ቢያገኙትስ። አንድ ፓኪስታናዊ የተሰረቀበትን ንብረት በፖሊሶች እጅ አገኘ መባሉን ሰማን።

ታዲያ ይሄ ምን ይገርማል የፖሊስ ድርሻው የተሰረቀን መፈለግ እና ማግኘትስ አይደል ሊያስብል ይችላል። ሰየውንም የጨው ሀውልት አድርጎ ያስቀረው፤ የሀገሬው የዜና አውታሮችንም የፊት ሽፋን የያዘው ታሪክ እንዲህ ነው።

ሰውየው በፓኪስታን በላሆር ሙጋልፑራ አካባቢ የሚኖር ሰው ነው፤ ኢምራን ይባላል። በፓኪስታን በፖሊሶች መዝገብ በዝቶ ከሚመዘገበው ሪፖርት ዋነኛው ሞተር ሳይክሌ ጠፋብኝ የሚለው ነው። ታዲያ ኢምራንም ይኽው ክፉ እጣ ይደርስበታል። ከዛሬ ስምንት ዓመታት በፊት ሞተር ሳይክሉን ካስቀመጠበት ያጣዋል። ካስቀመጠበት ሞተሩን የተሰረቀው ኢምራን ለፖሊስ እባካችሁ ሞተሬ ጠፍቶብኛል እና አድናችሁ አግኙልኝ ሲል ማመልከቻ ያስገባል።

ቢጠብቅ ቢጠብቅ ጅብ የበላው ሞተሩ ከዚህ አለ የሚለው ጠፋ። እሱም ተስፋ ቆርጦ ወደ ኑሮው ይመለሳል። ከስምንት ዓመት በኋላ ዛሬ ላይ ታዲያ ከትራፊክ ፖሊሶች የቅጣት ደረሰኝ በአድራሻው ይደርሰዋል። በትኬቱ ላይ ባየው ነገር ቆሌው ይገፈፋል።

ከስምንት አመት በፊት ተፋብኝ ባላት ሞተር ብስክሌቱ ላይ የአካባቢው የፖሊስ አዛዦች ተቀምጠው ሲጋልቡት የሚያሳይ ከደህንነት ካሜራ የተወሰደ ፎቶም በላዩ ላይ አለ።

ፓኪስታን ኤሌክትሮኒክ የትራፊክ መቅጫ መንገድን ትከተላለች። ግለሰቡ የትራፊክ ድንብን ሲጥስ የሚያሳይ ፎቶን አብሮ በማበር የቅጣትት ደረሰኞችን ለዜጎቿ በቤታቸው ታደርሳለች።

በነገሩ የደነገጠው ኢምራን ዓለም ይፍረደኝ እያለም ይገኛል። የጠፋን ያፋልገኛል ሰራቂውን ይይዝልኛል ያለው ፖሊስ የራሱ የሆነውን ንብረቱን ሲገለገልበት በማየቱ መበሳጨትም ተዘግቧል።

በሳምሶን ገድሉ
2022-06-07