በጋምቤላ ከተማ ከዛሬ ማለዳ ጀምሮ ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ እንደነበር ክልሉ አስታወቀ፡፡
ግርግሩ የተነሳው መንግሥት ሽብርተኛ በተባለው በሸኔ ወታደሮች እና በጋምቤላ ነፃነት ግንባር መካከል መሆኑ ተገልጿል፡፡
በጋምቤላ ከተማ ከጠዋቱ 12 ሰዓት ከ 30 ጀምሮ ሲካሄድ የነበረው የተኩስ ልውውጥ እስከ ረፋዱ 4 ሰዓት የቆየ ሲሆን የመንግሥት ኃይል ባካሄደው ትግል ከተማውን በከፊል ነፃ ማውጣት ተችሏል፡፡
የደረሰው ጉዳት በውል ባይታወቅም በሁለቱም ወገን ላይ ጉዳት መድረሱን የክልሉ መንግሥት አስታውቋል፡፡
በዮሴፍ ከበደ
2022-06-14
