ሀገሬ ቲቪ

የኢትዮጵያና የሱዳን ውይይት

ኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከሱዳን ሉዓላዊ የሽግግር ምክር ቤት ሊቀመንበር ሌተናል ጀነራል አዱልፈታህ አል ቡርሐን ጋር በናይሮቢ ተወያዩ።

ለኢጋድ ልዩ የመሪዎች ጉባኤ ነው መሪዎቹ ናይሮቢ የተገናኙት ። ኢትዮጵያና ሱዳን በድንበር የይገባኛል ጥያቄና በሕዳሴው ግድብ ምክንያት ሆድና ጀርባ ሆነው ቆይተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በማህበራዊ ትስስር ገፆቻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ሁለታችንም ያልተፈቱ ቀዳሚ ጉዳዮችን በሰላማዊ መንገድ በውይይት ለመፍታት ቁርጠኝነታችንን ገልጸናል ብለዋል።

በመቅደስ እንዳለ
2022-07-05