በያዝነው የምርት ዘመን 400 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማግኘት ታቅዶ የቅድመ ዝግጅት መደረጉ ተገለፀ።
ይህንን የተናገሩት የግብርና ሚኒስቴር የእርሻና የሆልቲካልቸር ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር መለስ መኮንን ናቸው።
በምርት ዓመቱ 13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ስለመታረሱም ሚኒስትር ዲኤታው ገልጸዋል።
ለማቅረብ ከታሰበው ከ15 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ 8 ሚሊዮን ያሀሉ ብቻ ለአርሶ አደሩ መቅረቡንም ተናግረዋል።
5 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በትራክተር ለማረስ ታቅዶም 2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሄክታር መታረሱንም ገልጸዋል።
በአብርሃም በለጠ
2022-07-19
