ሀገሬ ቲቪ

ሕንድ ለሁለተኛ ጊዜ ሴት ፕሬዚዳንት መረጠች

ሕንድ ባደረገችው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ድሮፓዲ ሙርሙን ፕሬዝዳንት አድርጋ መርጣለች ። ተመራጯ በሕንድ ታሪክ ሁለተኛዋ ሴት ፕሬዝዳንት ሲሆኑ፤ ሕንድን ላለፉት ስድስት ዓመታት በፕሬዝዳንትነት ከመሩት ራም ናት ኮቪንድ ሥልጣናቸውን ከሁለት ቀናት በኋላ እንደሚረከቡ ሮይተርስ አስነብቧል።

የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ወደ ተመራጯ ፕሬዚዳንት መኖሪያ ቤታቸው በማምራት የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን የሙርሙ ወደ ሥልጣን መምጣት በሚሊዮን የሚቆጠሩእንስት ሕንዳዊያንን ያበረታታል ሲሉ በትዊተር ገጻቸው አስፍረዋል።

በዮሴፍ ከበደ
2022-07-22