
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ) ዛሬ ባወጣው መረጃ ዓለም አቀፍ የእድገት ትንበያዎች ዋቢ በማድረግ በድጋሚ የመቀነስና ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት እንዲሁም የዩክሬን ጦርነት የሚያስከትለው አደጋ እየጨመረ እንዳለና ቁጥጥር ካልተደረገበት የዓለምን ኢኮኖሚን ወደ ውድቀት አፋፍ ሊገፋው እንደሚችል ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል።
ዓለም አቀፉ እውነተኛ የአዲሲቱ ዓለም ሀብት እድገት በሚያዝያ ወር ከወጣው 3.6 በመቶ ትንበያ ወደ 3.2 በመቶ እንደሚዘገይ የዓለም ኢኮኖሚክ አውትሉክ ባወጣው ማሻሻያ ላይ ገልጿል። አክሎም በቻይናና በሩሲያ ውድቀት ሳቢያ የዓለም ጥቅል ሀገራዊ ምርት ወይንም ጂዲፒ በሁለተኛውና በአራተኛ ሩብ ዓመት በከፍተኛ ደረጃ እንደተኮማተረ ገልጿል።
የእድገት ትንበያውን በሚያዝያ 2014 ዓ.ም ከነበረው 3.6 በመቶ በ2015 ዓ.ም ወደ 2.9 በመቶ ሊቀንስ እንደሚችል ከወዲሁ ተሰግቷል፡፡ ይህም ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ የሚያስከትለውን ውጤት ማሳያ ነው ይላል መረጃው።
በCOVID-19 ወረርሽኝ ምክንያት ቀደም ሲል በዓለም ኢኮኖሚ ላይ በርካታ ድንጋጤዎች ደርሰዋል። በዓለም ዙሪያ በተለይም በዩናይትድ ስቴትስና እንደ አውሮፓ ባሉ ኢኮኖሚያቸው በፈረጠሙ ሀገሮች ከሚጠበቀው በላይ ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት እንዲከሰት ሆኗል።
በ2012 ዓ.ም የCOVID-19 ወረርሽኝ ዓለም አቀፍ ውድቀትን ካሰከተለ በኋላ በ2013 ዓ.ም የዓለም እድገት ወደ 6.1 በመቶ ጨምሯል።
በመጠኑ ያገገመውን ኢኮኖሚ ከሚያዝያ ወር ጀምሮ ግን በእጅጉን አጨልሞታል። የዓለም ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ዋና ኢኮኖሚስት የሆኑት ፒየር ኦሊቪየር ለአንድ የዜና ኮንፍረንስ እንደገለጹት “ዓለም በቅርቡ በዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ውድቀት አፋፍ ላይ ልትገኝ ትችላለች ” ሲሉ ነገሩን አጠናክረውታል።
“የጥሩን ትንበያ ከዛሬው ጋር ካነጻጸርን ያለው ትልቅ ልዩነት ቢኖር የሩሲያ ወረራ በዩክሬን ላይ ሲሆን ይህም በዓለም ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ እያሳደረ ነው። እርግጥ ነው በአካባቢው ላይ ተፅዕኖ ያለው ሩሲያ እና ዩክሬን በመጀመሪያ እና በመጀመሪያ ደረጃ ተጎድተዋል። በኋላ ግን በንግድ ጣቢያዎች በኩል, በገንዘብ ምንዛሪ, ስደተኞች እና በተለይም የኃይል ንግድ በአውሮፓ ኢኮኖሚ ላይ እና በአካባቢው ሌሎች ምጣኔ ሃብቶችም በጣም ተጎድተዋል።”
“በዓለም ላይ ያሉት ሦስት ትልልቅ የኢኮኖሚ አንቅሳቃሾች ማለትም ዩናይትድ ስቴትስ፣ ቻይናና አውሮፓ በመደነቃቀፍ ላይ ናቸው ይህም ለዓለም አቀፉ ምጣኔ ሃብት ስጋት ነው” ሲሉ አክለዋል።
በቅርቡ የወጡ ትንበያዎች እንደሚያሳዩት በዩክሬን የሩሲያ ጦርነት የኃይል እና የምግብ ዋጋ ከፍ እንዲል በማድረግ አደጋ ላይ መውደቅን ያሳያሉ ተበሏል፤ ይህም የዋጋ ግሽበትን የሚያባብስ ከመሆኑም በላይ የገንዘብ ፖሊሲ ይበልጥ እንዲጠበቅ እና የዋጋ ግሽበት የቆይታ ጊዜ እንዲራዘም ያደርጋል።
ሩሲያ ወደ አውሮፓ የምትልካቸው የጋዝ አቅርቦቶች በዓመቱ መጨረሻ ላይ የሚቀንስ አሊያም የሚቋረጥ ከሆነ የዓለም የኢኮኖሚ ትንበያ በ2014 ዓ.ም ወደ 2.6 በመቶ፣ በ2015 ዓ.ም ደግሞ 2 በመቶ እንደሚቀንስ ከዚያ ቀጥሎ ባለው ዓመት ደግሞ በአውሮፓ እና በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ እድገት ዜሮ እንደስሚሆን ሮይተርስ የአይ ኤም አይፍን መርጃ በማጣቀስ ዘግቦታል።
በፍሬሕይወት ታደሰ
2022-07-27