ሀገሬ ቲቪ

ኮድ 2 ተሽከርካሪዎች ወደ ሥራ ሊገቡ ነው

የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ እና ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት አገራችንን ጨምሮ በበርካታ ሀገራት ላይ ያለ ችግር መሆኑ ይታወቃል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የነዳጅ እጥረትና መሰል ችግሮች የትራንስፖርት ዘርፉ ማህበረሰቡን በ አግባቡ እንዳያገለግል ምክንያት ሆኗል።

ይህን በትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች ላይ የሚስተዋልን ችግር ለመቅረፍ ዛይራይድ እና ወዝ የተባሉ የሜትር ታክሲ አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች የኮድ ሁለት ተሽከርካሪዎችን በስራ መውጫ እና በስራ መግቢያ ሰአት ፣ ለህዝብ አገልግሎት የሚሰጡበትን መንገድ አመቻችተው ወደ ስራ ሊገቡ መሆኑን አስታውቀዋል ።

በአዲስ አበባ ከተማ ከ100,000 በላይ የኮድ 2 መኪኖች ያሉ ሲሆን ፣ እነዚህን መኪኖች ለህዝብ አገልግሎት የሚሰጡበት መንገድ መመቻቸቱ ፣ ለከተማው የትራንስፖርት ችግር መፍትሄ ከማምጣቱ ባለፈ ፣ ለመንግስት በአመት ከታክሲ ዘርፉ የሚሰበስበውን ግብር ከ 3 ቢሊዮን እስከ 6 ቢሊዮን ብር ሊያደርሰው እንደሚችል የዛይራይድ ዋና ስራአስኪያጅ አቶ ሀብታሙ ታደሰ ኘሮግራሙን ባስታወቁበት መድረክ ላይ ገልጸዋል።

በዮሴፍ ከበደ
2022-08-05