ሀገሬ ቲቪ

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደቡብ አፍሪካ ገቡ

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን በአፍሪካ የሚያደርጉትን ጉብኝት ከደቡብ አፍሪካ ጀምረዋል።

ጉብኝቱ ሩሲያ በአፍሪካ ያላትን ተፅዕኖ ለማሳደግ የምታደርገውን ጥረት ለመገዳደር ነው ተብሎለታል። ባለፈው ወር የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ኢትዮጵያን ጨምሮ አራት የአፍሪካ ሀገራትን እንደጎበኙ ይታወሳል።

ሚኒስትሩ ከደቡብ አፍሪካ ወደ ዴሞክራቲክ ኮንጎ ቀጥሎም ወደ ሩዋንዳ ይሄዳሉ ተብሎ ይጠበቃል ። ዘገባው የሲጂቲኤን ነው።

በመቅደስ እንዳለ
2022-08-08