ሀገሬ ቲቪ

በትግራይ ክልል ለ20 ሺህ አባዎራዎች የአፈር ማዳበሪያ ድጋፍ ተደረገ

ዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ በትግራይ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች ለሚገኙ 20 ሺህ አባዎራዎች የአፈር ማዳበሪያ ድጋፍ አደረገ።

ኤን ፒ ኤስ የተሰኘ የአፈር ማዳበሪያ እና ዩሪያ ድጋፍ የተደረገላቸው አርሶ አደሮች በማዕከላዊ ፣ ምስራቅ እና ደቡብ ትግራይ የሚገኙ መሆናቸውን ከኮሚቴው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

ድጋፉ በግለሰብ ደረጃ 120 ሺህ ገደማ የሚደርሱ አርሶ አደሮችን ምርታማነት ለማሳደግ እንደሚያስችል ተጠቁሟል።

በዮሴፍ ከበደ
2022-08-09