ሀገሬ ቲቪ

የደቡብ አፍሪካ የልማት ማህበረሰብ ጉባኤውን እያካሄደ ነው

የደቡብ አፍሪካ የልማት ማህበረሰብ መሪዎች 42ኛ ጉባኤያቸውን በኪንሻሳ ጀምረዋል። በጉባኤው የሀገራት ትስስርን እና የአካባቢ ንግድን በማጠናከር ረገድ የተገኘው ውጤት ይገመገማል ተብሏል ።

የአካባቢ ሰላም ፤ የአግሮ ኢንዱስትሪ ፣ የማዕድን ሀብት ማበልጸግ እና ኢንዱስትሪዎችን ማስፋፋት በስፋት እንደሚመከርባቸው ተገልጿል ።በጉባዔው ማጠናቀቂያ ላይም ማላዊ የአመራር ቦታውን ለተረኛዋ ኮንጎ እንደምታስረክብ ተሰምቷል ።

በዮሴፍ ከበደ
2022-08-18