ሀገሬ ቲቪ

ለመጀመሪያ ጊዜ ከዩክሬን ለኢትዮጵያ የተላከው ስንዴ ጂቡቲ ገባ

ወደ ጅቡቲ የደርስው ስንዴ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አማካኝነት ለኢትዮጵያ የተላከ ነው ። ይህም ሩሲያ ዩክሬንን ከወረረች በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ አፍሪካ የተላከ ነው።

ጂቡቲ የደረሰችው መርከብ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአለም ምግብ ፕሮግራም የተገዛውን 23 ሺህ ቶን ስንዴ ይዛለች ።

የዓለም ምግብ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ቃል አቀባይ ክሌር ኔቪል እንደተናገሩት ስንዴው በጦርነት እና በአስከፊ ድርቅ ምክንያት የተጎዱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ነዋሪዎችን ለመመገብ የሚደረገውን ጥረት ይደግፋል ብለዋል።

በብሩክ ያሬድ
2022-08-30