ሀገሬ ቲቪ

ኒውዮርክ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጀች

ኒው ዮርክ የፖሊዮ ስርጭትን በመስጋት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጀች። የበሽታ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማዕከል (CDC) በቆሻሻ ውኃ ላይ ባደረገው ጥናት በኒውዮርክ በርካታ ቦታዎች የቫይረሱ ናሙናዎችን ማግኘቱን ይፋ አድርጓል ።

በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይም አንድ ሰው በፖሊዮ ቫይረሱ መያዙ ተረጋግጧል ። ለዚህ ነው ኒውዮርክ በፖሊዮ ሳቢያ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለማውጅ የተገደደችው ።

ፖሊዮ በአሜሪካ ሲታይ ከአስርት ዓመታት በኋላ ነው ተብሏል። አሜሪካ የዛሬ 50 ዓመት በፊት ነበር ከፖሊዮ ነጻ ሀገርነቷን ያውጀችው።

በብሩክ ያሬድ
2022-09-12