ሀገሬ ቲቪ

የአዲሱ የኬንያ ፕሬዝዳንትነት ዊልያም ሩቶ በዓለ ሲመት ተከናወነ

በኬንያ ምርጫ አሸናፊ የሆኑት ዊልያም ሩቶ የፕሬዝዳንትነት ቃለ መሃላቸውን ፈጸሙ። የ55 ዓመቱ ሩቶ 5ኛው የሀገሪቱ ፕሬዘዳንት ሆነው ቃለ መሃላቸውን ሲፈጽሙ በርካታ ኬንያውያን በስታዲየም ተግኝተው ደስታቸውን ገልጸዋል ።

በጠባብ ውጤት በምርጫው የተሸነፉት ራይላ ኦዲንጋ በስነ ስርዓቱ ላይ አልታደሙም። 50 ነጥብ 5 ለ 48 ነጥብ 8 በመቶ በሆነ ውጤት የተሸነፉት ራይላ ኦዲንጋ ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት የወሰዱት ቢሆንም ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ምርጫውን ፍትሃዊ ነው ብሎ ጥያቄያቸውን ውድቅ እንዳደረገው የሚታወስ ነው።

በበዓለ ሲመቱ ላይ ለመታደም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አቢይ አህመድን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት መሪዎች ታድመዋል።

በአብርሃም በለጠ
2022-09-13