ሀገሬ ቲቪ

ዛምቢያ 43 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ከሀገሯ አስወጣች

የዛምቢያ የስደተኞች ባለሥልጣን 43 ኢትዮጵያዊ ስደተኞችን ማባረሩን ገለጸ።

ስደተኞቹ በሕገወጥ መንገድ ወደ ዛምቢያ መግባታቸውን ተከትሎ በፍርድ ቤት የተወሰነውን የቅጣት ገንዝብ ከከፈሉ በኋላ ነው ከዛምቢያ እንዲወጡ የተወሰነው።

20 የሚኾኑት ወንድ ስደተኞች ከ 15 እስከ 35 በሚሆን የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ናቸው።

ከመስከረም 8 / 2020 ጀምሮ እስካሁኑ በተወሰደ እርምጃ 344 የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን በሕገወጥ መንገድ ወደ ዛምቢያ እንደገቡ በመረጋገጡ ከሀገሪቱ እንዲወጡ መደረጋቸውን ሲጂቲኤን አስነብቧል።

በሙሉጌታ በላይ
2022-10-13