ሀገሬ ቲቪ

ለዩክሬን ወግነው ድምጽ የሰጡት የማዳጋስካር ውጪ ጉዳይ ሚንስትር ተባረሩ

የማዳጋስካር ፕሬዝዳንት አንድሪ ራጅላይና የሀገሪቱን ውጪ ጉዳይ ሚኒስተር ማባረራቸው ተሰማ ።

የውጪ ጉዳይ ሚንስትሩ የተባረሩት ሩሲያን ለማውገዝ በተጠራው የተባበሩት መንግስታት ጉባኤ ላይ ዩክሬንን ደግፈው ድምጽ በመስጠታቸው ነው ።

ሩሲያ የዩክሬንን አራት ግዛቶች መጠቅለሏን ተከትሎ በተጠራው ጉባኤ 143 ሀገራት ሩሲያን ማውገዛቸው ይታወሳል ።

የድጋፍ ድምጹን ከሰጡት መካከልም የማዳጋስካር የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር መገኘታቸው የሀገሪቱን መሪ በእጅጉ አበሳጭቷል ።

ውጪ ጉዳይ ሚኒስተሩ ድምጹን በሰጡ ማግስት በሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ማንንም ሳያማክሩ እንዳደረጉት የተነገረ ሲሆን አሁን ደግሞ መባረራቸውን አፍሪካን ኒውስ አስነብቧል።

በዮሴፍ ከበደ
2022-10-20